የስንዴ ፍላጎትን በአገር ውስጥ የመሸፈን ግብግብ


ኢትዮጵያ የስንዴ ፍላጎቷን በአገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን የምታደርገው ጥረት ትክክለኛ አቅጣጫ የተከተለና ለውጤት እያበቃን ስለመሆኑ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል። ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን ስንዴ በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት በርካታ ሥራዎች እያከናወነች ትገኛለች።

ለዚህም ደግሞ የኩታ ገጠም የግብርና ሥራና የመስኖ ልማት ሥራዎች እየተካሄዱ በመሆናቸው አገሪቱ በትክክለኛ የግብርና አቅጣጫ ላይ መሆኗን የሚያሳይ ንቅናቄ መፍጠር ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያ ለስንዴ ምርት የሚሆን ከፍተኛ የውኃና የመሬት አቅርቦት እንዳላት በዘርፉ የተሰማሩ ምሁራን ሲናገሩ ይደመጣል፤ይህንን ዕድል በአግባቡ ተጠቅሞ ከራስ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው፡፡

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ኢትዮጵያ የስንዴ ፍላጎቷን በአገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን ብሎም ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬን ለማግኘት እንዲቻል በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አመራሮች ልዩ ትኩረት ሰጥተው ክትትል እንዲያደርጉ አቅጣጫ ከመስጠታቸው ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ የደረሰበትን ደረጃ እየጎበኙ ይገኛሉ፡፡

አገሪቱ በስንዴ እርሻ ሥራ ላይ እያሳየች ያለውን ጥረት ማስፋት ከቻለች በአጭር ጊዜ ውስጥ ‘በምግብ ራስን መቻል’ የሚለውን ትልቅ እቅድ ማሳካት እንደሚቻል ከመጠቆሙም በላይ ለውጭ ንግድ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶችም ሊኖሩ እንደሚችሉ ያሳዬ ነው።

መንግሥት አሁንም ለዘርፉ እድገት ትኩረት በመስጠት በተለይም ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ያለው ማዳበሪያ ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት ያሳዬ ነው፡፡

አርሶ አደሩ ትክክለኛውን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀም በየዕለቱ ድጋፍ ማድረግ፤ ተመራማሪዎች ከአከባቢው ሥነ-ምህዳር ጋር ተስማሚ የሆኑ መፍትሄዎችን ማአርሶ አደሩ ትክክለኛውን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀም በየዕለቱ ድጋፍ ማድረግ፤ ተመራማሪዎች ከአከባቢው ሥነ-ምህዳር ጋር ተስማሚ የሆኑ መፍትሄዎች ማስቀመጥ ይገባል።

በስንዴ እርሻ የተሰማሩ አርሶ አደሮችም ሆኑ ባለሃብቶች ከመንግሥትና ከግብርና ባለሙያዎች የሚቀርቡላቸውን ምክረ ሃሳቦች በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ ምርታቸውን ማስፋት ይኖርባቸዋል። በስንዴ ምርት ላይ ያለውን የትኩረት ተደራሽነት በማስፋት የዘርፉን ምርትና ምርታማነት ለማስፋት መጣር ይገባል።

መንግሥት ከውጭ የሚገባውን ስንዴ በአገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን በአፋር፣ በኦሮሚያና በደቡብ እና በሌሎችም አካባቢዎች በሚገኙ ሥፍራዎች ላይ የበጋ ስንዴ ልማት ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

prosperity

Published by Admin

This site is created to strengthen the information flow between our residents and the government. Kolfe woreda 6 is located in Kolfe keranio subcity, Addis Ababa, Ethiopia.

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started