ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጠናቀር ጽንፈኛነትን በመታገል የኢትዮጵያን ብልፅግና እናረጋግጣለን!!

እኛ ኢትዮጵያን እንደ ድር እና ማግ የተሳሰረ እና የተሰናሰነ ማንነት ያለን ህዝቦች ነን ።ይህንም ሀገራችን የብዝሃ ማንነት፣ሃይማኖት እና ባህልን ባለቤት መሆኗ የሚታወቅ ሀቅ ነው። አባቶቻችን በአድዋ እና ካራ ማራ ላይ በዘመኑ የነበሩ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው ለጋራ አላማ እና ለሀገር ነፃነት ሲሉ በጋራ መስዋዕትነት ከፍለው ሀገር ከነ ክብሩ እና ዳር ድንበሩ ጠብቀው ለዚህ ትውልድ ማስተላለፍ ችለዋል ።እኛ ኢትዮጵያውያንም የአባቶቻችንን አድዋ እና ካራ ማራ ታሪክ ዛሬ ላይ በአንድነት ፣በወንድማማችነት/እህትማማችነት እሴት፣ በህብረብሄራዊ አንድነት ፣በብዝሃ ሀይማኖት አንድ ሆነን ልዩነቶቻችንን ውበታችን አድርገን የጽንፈኝነት በጋራ መታገል ይገባል ።

የዚህ ዘመን ትውልድም የአባቶቹን ፈለግ በመከተል የኔ ብቻ ከሚል የጽንፈኝነት አስተሳሰብን ለሀገር ብልፅግና እና እድገት ፀር ሆኖ አንድ እርምጃ ወደ ፊት ሁሉት እርምጃ ወደ ኋላ ሲመልሰን የቆየ ኋላ ቀር አስተሳሰብ መሆኑን በመረዳት የዚህን ዘመን ትውልድ ትብብርን እና አብሮነትን በማጎልበት ዘመኑን የመዋጀ እና ሊመጥን የሚችል አስተሳሰብ በመገንባት ከኃላ ቀር እና ጎታች አስተሳስብ በመውጣት የጋራ እና አሰባሳቢ የሆኑ የወል ታሪኮችን በመገንባት በጋራ ለሁሉም የምትሆን ኢትዮጵያን መገንባት ለመጭው ትውልድ በሁሉም መስክ የበለፀገች እና በህብረ-ብሔራዊት መንፈስ የተገነባች ኢትዮጵያን የማውረስ አደራ የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል።

መልካም ቀን ይሁንልዎ!

kolfe_prosperity_party- ብልፅግና

ድጋፍና ክትትል

ጠንካራ ፓርቲን በመፍጠር የሴቶች እና የዜጎች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የውስጠ ፓርቲ ስራዎች ተቋማዊ ሆነው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ሴቶች አይተኬ ሚናን እየተጫወቱ ይገኛሉ።

ሴቶች በበርካታ የልማት እና ማህበራዊ ተግባራት ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው ዕለት የብልፅግና ፓርቲ ኮ/ቀ/ክ/ከተማ ቅ/ፅ/ቤት ሴት ሊግ አስተባባሪ ወ/ሮ ያለምወርቅ ዳኘው በተገኙበት በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 6 ብልፅግና ፓርቲ ሴት ሊግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ዙሪያ ድጋፍና ክትትል ተደርጓል።

በክ/ከተማው ባሉ ወረዳዎች የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች፣ የወረዳው ሴት ሊግ ስራ አስፈፃሚዎች፣ መሠረታዊ ፓርቲ አመራሮች፣ ህዋስ አመራሮች እና አባላት በተገኙበት በተካሄደው ድጋፍና ክትትል ፓርቲውን ለማጠናከር እና ተቋማዊ አሰራርን አስጠብቆ ከመሄድ አንፃር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በስፋት ታይተዋል።

በሌላ በኩል ሴቶች በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚው ዘርፍ ያላቸው ተሳተፎ በተለይ በስራ ዕድል ፈጠራ እና ከራሷ አልፋ ለሌሎች መትረፍ ላይ የተሰሩ ስራዎች ምን እንደሚመስሉ በድጋፍና ክትትሉ ተመላክቷል።

በመጨረሻም በወረዳው ሴት ሊግ የተከናወኑ ሌሎች ወረዳዎች ልምድ ሊወስዱባቸው የሚገቡ ጉዳዮች መኖራቸው የተመላከተ ሲሆን ለውጥ የታየባቸው ነገር ግን ሙሉ ያልሆኑ ጉዳዮች ላይም በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የብልፅግና ፓርቲ ኮ/ቀ/ክ/ከተማ ቅ/ፅ/ቤት ሴት ሊግ አስተባባሪ ወ/ሮ ያለምወርቅ ዳኘው አሳስበዋል።

Design a site like this with WordPress.com
Get started