“ዛሬ የምናያቸውና የምንረማመድባቸው መንገዶች በአንድ ወቅት ጢሻ የነበሩና በፊት ቀደሞች መሥመር የወጣላቸው ናቸው። ዛሬ የሰለጠኑ ሀገሮች የሥልጣኔ ከፍታ ላይ የደረሱት በአንድ ወቅት ፊት አውራሪዎቻቸው በመከራ ውስጥ አልፈው፣ ችግር እና ፈተናውን ተሻግረው መሠረት ስላኖሩላቸው እንጂ አዲስ ተዓምር ተፈጥሮላቸው አይደለም።
ድኅነት፣ መታደስና ብልጽግና የሚመጣው ፊት ቀዳሚዎች ችግርና መከራውን ተጋፍጠው መንገድ ማስመር ሲችሉ ብቻ ነው። እኛ የዛሬው ትውልዶች ለሀገራችን ፊት ቀዳሚዎቿ እንደሆንን ማመን ይገባናል።
እኛ መከራዋን ሳንቀበል ለኢትዮጵያችን ምቾት፣ ዝቅታውን ሳናይ ለሀገራችን ከፍታ፣ ጭለማውን ሳንጎበኝ ለልጅ ልጆቻችን ብርሃን እንደማይመጣ ማወቅ አለብን።”
የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
