ያለፉ ችግሮችን በማንሳት ከመወቃቀስ በመፍትሄ አጀንዳዎች ዙሪያ አተኩሮ መስራት አለበት-የሰላም ሚኒስትሩ


(ኢ.ፕ.ድ)

የአሁኑ ትውልድ ያለፉ ችግሮችን በማንሳት ከመወቃቀስ ወጥቶ ለቀጣይ መፍትሄ ማስቀመጥ በሚያስችሉ አጀንዳዎች ዙሪያ አተኩሮ መስራት እንዳለበት የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ።

”አካታች ብሄራዊ ምክክሩን ከማሳካት አንፃር የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ ሚኒስቴሩ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ተጀምሯል።

የምክክር መድረኩ ሲጀመር ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ባለፉት በርካታ ዓመታት የመጠላለፍና የመነቃቀፍ ፖለቲካ ሲካሄድ ቆይቷል።

በዚህም የዜጎች የሰላም እጦት፤ ተረጋግቶ ያለመኖር እና ለበርካታ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች መዳረጋቸውን ገልጸዋል።

ይህንኑ የመነቃቀፍና የመጠላለፍ ፖለቲካ ለማስወገድ የአሁኑ ትውልድ ያለፉ መጥፎ ታሪኮችን በማስታወስ መቆዘም ሳይሆን ለቀጣይ ትውልድ መፍትሄ ሊሆን በሚችሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ባለፉት መንግስታት ዴሞክራሲን ለይስሙላ ሲጠቀሙ በመቆየታቸው በሃገሪቱ የዳበረ ዴሞክራሲ መገንባት አለመቻሉን አውስተዋል።

አሁን ላይ ህዝቡን በጋራ ሊያግባባ የሚችል ብሄራዊ አካታች ምክክር በማስፈለጉ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህ ደግሞ መላ ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን በጎ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ ይገባል ነው ያሉት።

ብሄራዊ ምክክሩ ቢቻል ሁሉንም ሊያግባባ በሚችል አግባብ እንደሚከናወን ገልጸው፤ አሊያም ለቀጣዩ መልካም የስርዓት አቅጣጫ ቀይሶ ማለፍ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

ለዚህም የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ዘመኑን የሚመጥን ሃሳብ በማፍለቅና አቅጣጫዎችን በማሳየት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አቶ ብናልፍ አመልክተዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ዘውዱ እምሩ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የውጭ ጠላት ወረራን በድል ልትወጣ የቻለቸው ከብሄርና ከዘር የፀዳ ፅኑ ብሄራዊ አንድነት በመኖሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የውጭ ጠላት የቱንም ያህል ቢጥር የውስጥ አንድነት ጠንካራ እስከሆነ ድረስ ተፅዕኖ ሊፈጥር አይችልም ብለዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጰያ ላለችበት ሁኔታ የውስጥ አንድነት ከመላላ ጋር ተያይዞ የመጣ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ጠንካራ ብሄራዊ አንድነት መፍጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ በምክክር መድረኩ የሰላም ሚኒስቴርና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮች እንዲሁም ምሁራን፣ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን በምሁራን እየቀረቡ ባሉ ጥናታዊ ፅሁፎች ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት እስከ ህብረት


ቀደም ሲል የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ያሁኑ የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተው በኢትዮጵያ ሲሆን የተቋሙ መቀመጫም የሆነው በመዲናችን አዲስ አበባ ነው፡፡የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመጀመሪያው መሪ የሆኑት ቀዳማዊ ሃይለስላሴ መሆናቸውን በታሪክ ሰፍሮ እናገኘዋለን።

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል እንደመሆኗም በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአፍሪካ ነጻነት ድምጽ በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስታደርግ መቆየቷ በበርካታ አፍሪካዊያን ምሁራኖች አንደበት ሲገለጽ ቆይቷል፤ወደፊትም ይህ እውነታ ለትውልድ የሚተላለፍ ይሆናል፡፡

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ወደ አፍሪካ ሕብረት ከተሸጋገረም በኋላ በአፍሪካ ውስጥ ለሚነሱ ግጭቶች በሠላም ማስከበር እና በሌሎች ልዩ ልዩ ተልዕኮዎች ስትሳተፍ ቆይታለች፤ እየተሳተፈችም ትገኛለች። ኢትዮጵያ እንደ መስራች አገር የመሪነት ሚናዋን በፍጹም ቁርጠኝነት ኃላፊነቷን እየተወጣች ትገኛለች።

ምዕራባውያን ኢትዮጵያን ላይ ከፍተኛ ጫና እያደረጉ ባሉበት ወቅት አፍሪካውያን 35ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው በአዲስ አበባ እንዲካሄድ መወሰናቸው ለኢትዮጵያ ያላቸውን ክብርና ታላቅነት ያሳያል፡፡

አፍሪካውያን፣ የአፍሪካ ምሁራን እና መንግሥታት ለኢትዮጵያ የሚሰጡት ክብር ከፍ ያለ መሆኑን አንዱ ማሳያ አፍሪካውያን 35ኛው የሕብረቱ ጉባኤ በአዲስ አበባ እንዲካሄድ መወሰን መቻላቸው ነው፡፡

እኛ አፍሪካዊያን ከድህነት የመውጣትና የማደግ ተስፋችን እር በእርስ የተጋመደና የተሳሰረ ነው፡፡ አንዳችን ያለአንዳችን ከድህነት መውጣት በእጅጉ ይከብደናል፤ስለሆነም አፍሪካችንን ወደ ብልጽግና ከፍታ ለማሸጋገር ያስችለን ዘንድ አህጉራዊ ግንኙነታችንን ይበልጥ ማጠናከር ይገባናል፡፡

ኢትዮጵያ የአፍሪካዊያን ሁለተኛ አገራቸው ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ አዲስ አበባ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ህንጻ ደግሞ አፍሪካዊያን በልዩ ልዩ ጉዳዮቻቸው ዙሪያ ከየአገራቸው ወደ መዲናችን መጠው የሚመክሩበት የጋራ መጠለያቸው ነው፡፡

አፍሪካውያን ወንድሞቻችን አገራችንን እንደ እኛ ይወዳሉ። የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በዓለ ሲመት ወቅት ከተገኙት ጎረቤት አገራት መካከል የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ‹‹ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት እናት›› በማለት መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

እንደ አገር ብቻችንን ከድህነት አረንቋ መውጣት ከባድ ነው፤ሊታሰብም አይችልም፡፡የወደፊት ራዕያችንና እጣ ፈንታችን ከአፍሪካዊያን ጋር የተሳሰረ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2063 የአፍሪካ አገራትን እርስ በእርስ በልማት የማስተሳሰር ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ከተገባ ዋል አደር ብሏል።ይህን ዕቅድ ከግብ ማድረስ ስንችል አብሮ የመልማትና የማደግ የጋራ ዕቅዳችን ይሳካል ሲሉ ገልጸዋል ማለት ነው፡፡

የ35ኛው የህብረቱ አባል አገራት ተሳታፊ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን ወደ አዲስ አበባ ከመጡ ቀናቶች ተቆጥረዋል፤ስለሆነም የቆይታ ጊዚያቸው ልክ አገራቸው እንዳሉ እንዲሰማቸው ማድረግ የእያንዳንዳችን ግዴታና ሃላፊነት መሆኑን ተረድተን በዚህ ልክ መዘጋጀት ይገባናል።

ከአፍሪካውያን ይልቅ ለነጮች ያለን ከበሬታ በእጅጉ የተለዬ በመሆኑ ይህንን የተዛባ አተያይ በፍጥነት መቀልበስና ለአፍሪካዊያን ያለን ምልከታ ማሰተካከል ይኖርብናል፡፡

የአፍሪካ ወንድሞቻችን ከእኛ ጋር መሰለፋቸው አንዱ ማሳያ አሜሪካን ጨምሮ ሌሎች ምዕራባዊያን አገራት ከአሸባሪው ህወኃት ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ እያሳደሩት በነበረው ጫና ላይ የይበቃል (No More) እንቅስቃሴ በመቀላቀል ከፍ ያለ አጋርነታቸውን ማሳየታቸው ነው፡፡

ስለሆነም ለአፍሪካዊያን ያለን ምልከታ ያደገና ወቅቱን ያገናዘበ መሆን እንደሚገባው መረዳት አለብን፡፡በጉባኤው ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ በሚመጡበት ጊዜ ኢትዮጵያን እንደሚያስቧት የአፍሪካውያን መሆኗን በአክብሮትና የእንግዳ ተቀባይነት ባህላችንን ማሳየት በእርግጥም ለአፍሪካዊያን ያለንን ወዳጅነት ከፍታ ማሳያ ይሆናል።

አዲስ የአፍሪካ የተስፋ ፀዳል!


ፓን-አፍሪካኒዝም ቀደምት የአፍሪካ አባቶች የጀመሩት ቀኝ ገዥዎች ባሰመሩልን የግዛት መስመር ተከፋፍለን ብዙ ትንንሽ ፤ደካማ እና ድሃ ሃገራት ሆነን ሃብታችንን ፤ጉልበታችንን እና እውቀታችንን ከምናባክንና ከምንበዘበዝ ፤ አንድ ታላቅ አፍሪካዊ ህዝብ ሆነን ራሳችንንም ህዝባችንንም ታላቅ እናድርግ ፤ የራሳችንምም ሃብት በራሳችን እንጠቀም፤ ከኛ አልፎ ለአለም የሚበቃ የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ሃብት አለን የሚል ሩቅ ተሻጋሪ አስተሳሰብ ነው፡፡
ይህ ብዙዎችን ከየአቅጣጫው ያሰባሰበና ያነቃ ሃሳብ መተባበርን እና ህብረትን በህዝቦ መሃከል ጠንካራ ግንኙነትን በመፍጠር ሁሉም ያለውን አቅም አሰባስቦ በሁሉም ረገድ ተፅእኖ ፈጣሪ አፍሪካን እውን የማድረግ ትልም ነው፡፡
አንድ ስንሆን እንደመጣለን፤ ተፅእኖ መፍጠር እንችላለን የትኛውም ውጫዊ ሃይል ለራሱ ሲል በአክብሮት ይፈልገናል፤ ተፅእኖም መፍጠር ያስችለናል የሚል ቅኝት ያለው ነው፡፡
እውነትም ነው፡፡ አፍሪካ እጅግ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ብዙ መልከ ብዙ የልማት አቅሞች ታቅፋ ያለች አህጉር ናት፡፡ ነገር ግን ተፈጥሮ ያደላትን እምቅ ሃብት መጠቀም እንኳን ሳትችል፤ የበይ ተመልካች ሆና ልጆቿ በብዙ ፈተናዎች እና እርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ሲማቅቁ ፤በስደት ኑሯቸውን ሲገፉ ኖረዋል፡፡
የፓንአፍሪካኒዝም ሃሳብ አፍሪካን ከሩቅ ሆነው መቀራመት በሚፈልጉ ሃይሎች ዘንድ ግን እንደ ስጋት ታይቶ ብዙ ፈተናዎችን አስተናግዷል፡፡
ለአስተሳሰቡ ዳግም ልእልና ኢትዮጵያ እንደ ቀደመው ጊዜ ሁሉ የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት የኢትዮ- ኤርትራ ችግር በአስደናቂ መንገድ በሰላም እንዲፈታ ከማድረግ ጀምሮ ለፓን አፍሪካኒዝምን አስተሳሰብ በተቃኘ ስሜት የደቡብ ሱዳኑን ችግር በመፍታት በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የድንበር ውዝግብ ውስጥ የነበሩ ሃገራትን በሙሉ በማወያየት እና በማስማማት የግንኙነቱም መረብ ድር ማስመር ጀምረዋል፡፡
ሃገራት ድንበር ዘለል በሆነ አስተሳሰብ ቀጠናዊ የኢኮኖሚ ትስስርንም (Economic Integration) የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የቋንቋ የባህል ግንኙነቶች እንዲዳብሩም ከመሪዎች ጋር መክረዋል አስደናቂ የትብብር መንገድንም እንደ አዲስ ከፍተዋል፡፡
“እኔ መላ አፍሪካን አንድ የማድረግ ህልም አለኝ “ ሲሉ በአንድ ወቅት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የፓን አፍሪካኒዝም ለአፍሪካ ወዳጆች አዲስ ጀግና አዲስ የተስፋ ፀዳል ሲሆን ለዘመናዊው ቀኝ ገዥዎች ግን ዳግም መርዶን ያዘለ ነበር፡፡
ከዚያም አልፎ ኢትዮጵያ ውስጥ ተላላኪ መንግስት አይፈጠርም፤ የራሳችንን መንግስት በራሳችን መምረጥ አለብን፤ የሚሉትና ሌሎችም ሃሳቦች ለነዚህ በአፍሪካውያን ሉአላዊነት እና እኩልነት ለማያምኑ ሃይሎች የሚዋጥላቸው አልሆነም ይህች ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም በሚል ሃሳብ ኢትዮጵያ ላይ ባለ አቅማቸው ሁሉ ዘምተዋል፡፡
ሆኖም ግን ኢትዮጵያ በውጪ ቀኝ ገዥ ሃይሎች የተከፈተባትን ጦርነት በመመከት ዳግም አድዋዊ ትውልድና ፓንአፍሪካዊት አገር ሆና አንፀባርቃለች፡፡
አፍሪካውያንም የኢትዮጵያን ጥሪ ሰምተው #NoMore ንቅናቄ ከጎናችን መሆናቸውን ያሳዩ ሲሆን የህብረቱም ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲካሄድ በማድረግ ታሪክ የማይዘነጋው ፓንአፍሪካዊ ውሳኔያቸውን አሳርፈዋል ፡፡
ይህም ዳግም የአፍሪካን ልደት የሚያበስር የመቺውን ዘመን ብርሃናማነት የሚናገር አፍሪካዊ የምስራች ነው!!

‹‹በኢትዮጵያ የሚካሄደው የመሪዎች ጉባኤ የአፍሪካውያንን አንድነትና ወንድማማችነት ያረጋገጠ ነው›› –

ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር

35ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ በኢትዮጵያ መዲና መካሄድ የአፍሪካውያንን አንድነትና ወንድማማችነት ያረጋገጠ ነው ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ገለጹ። የአፍሪካውያን አንድነት ለአገራዊና አህጉራዊ ጠላቶች ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል።

ዶክተር ቢቂላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ 35ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በኢትዮጵያ መዲና መካሄድ የአፍሪካውያን አንድነትና ወንድማማችነት የሚያጠናከርና ለውጭ ኃይሎች ትልቅ መልዕክት ያስተላለፈ ነው።

አገር በማዳን ዘመቻ መንግሥት ጦርነት ውስጥ በገባበት ጊዜ የኢትዮጵያ ጠላቶች ከውስጥና ከውጪ ተደራጅተው በሚዲያ፣ በኢኮኖሚና በዲፕሎማስ መስክ ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ አካሂደዋል።

ሚዲያቸውን በመጠቀም ከሁለት ሦስት ወር በፊት ኢትዮጵያ ልትበተን ነው የውጭ አገር ዜጎች አፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ ላይ እምነት እንዳይኖራቸው ለማድረግ መጠነ ሰፊ የተዛባመረጃ አሰራጭተዋል ብለዋል። ተቋማት በኢትዮጵያ ውስጥ ያላቸውን የልማትና የዲፕሎማሲ ሥራዎቻቸውን አቋርጠው እንዲወጡም ጥረት ተደርጎ እንደነበር አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በአንድነት በመቆም በከፈሉት መስዋዕትነት አገራዊና አህጉራዊ ጦርነቱን በሚገባ መቀልበስ ተችሏል ያሉት ዶክተር ቢቂላ፤ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በጦርነቱ ምክንያት ያጣችውን ንብረት ወደ መገንባት እየተጓዘች ትገኛለች

ብለዋል። ድሉ የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ በኢትዮጵያ መዲና እንዲካሄድ በማስቻሉ እንደ አገርም ሆነ እንደ አህጉር ለውስጥና ለውጭ ጠላት ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል ብለዋል። የአፍሪካውያን አንድነትና ወንድማማችነትም የጥንካሬ ማሳያ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

እንደ ዶክተር ቢቂላ ገለጻ፤ ይህ ሁሉ ዘመቻ በኢትዮጵያ ላይ በተከፈተበት ወቅት አብዛኛው የአፍሪካ አገራት በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ድምፃቸውን በማሰማት ከኢትዮጵያ ጎን ቆመው አሳይተዋል። ኢትዮጵያ የገጠማትን የውስጥ ችግር በራሷ አቅም መፍታት እንዳለባት ያሰሙት ድምፅም በተዘዋዋሪ አፍሪካውያን የራስን ጉዳይ ያለማንም የውጭ ኃይል ጣልቃ ገብነት መፍታት እንደሚችሉ ትልቅ ትርጉም ያለው መልዕክት አስተላልፈዋል ብለዋል።

አፍሪካውያንና ኢትዮጵያውያን በከፈሉት መስዋዕትነት የኢትዮጵያ እውነታ ለዓለም ማኅበረሰብ ተገልጧል። በኢትዮጵያ የሠላምና የጸጥታ ችግር አለመኖሩ በአፍሪካ ኅብረት ተቀባይነት አገኝቶ 35ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዲካሄድ መወሰኑ ለዚህ ትልቁ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። ድሉ የኢትዮጵያውያንና የአፍሪካውያን ድል ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ጥንካሬውን ለማስቀጠል የውጭ ጣልቃገብነትን በመቃወም የአፍሪካውያንን አንድነት ለማጠናክር የጀመረውን ፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ለማጠናከር ይሠራል ያሉት ዶክተር ቢቂላ፤ ለወደፊት አፍሪካዊ አንድነትን ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ትስስሮች ለማጠናከር እንደሚሠራ ገልጸዋል።/epa/

After Three Years, What is New in Addis?

By Maraki Ayalew
As we are a few days away from the 35th summit of AU (Head of States and Governments), it is necessary to shed light on how the host city, Addis Ababa is different this time. After three years of pause, due to covid-19 Addis Ababa, Addis for short is ready to host the historical summit of AU as usual. Well, one might ask, did Addis change within these three years? The answer will be YES, the past three years were not only about overcoming the challenges caused by covid-19 or reversing threats of national unity. Against all the odds within these three years, Addis has got a completely new look with new features like eco-parks, recreation centers, high rising buildings, etc.
When talking about the last three years of change in Addis, it is difficult not to mention The Unity Park, which is located within The Grand Place. The park was established in 2019, it contains historical buildings, different floras, animals, mosaics, etc. It will take hours to walk through and visit the features in the park. For sure spending time in this park is rewarding.
Friendship square is becoming another feature of Addis in the last three years. The landscape and its location along with other features gave the park a sparkling view. It is located in front of the Sheraton Addis Hotel. When talking about parks, there are also Africa, Ethiopia and Addis Ababa Park within a walking distance from Unity Park or Friendship Square. Though, these parks were there for years the renovation works done recently gave parks new attractive features.
Last but not least, Entoto is another new feature Addis acquired in the last three years. It is an eco-friendly recreation center on the top of Entoto hill, which is found at the northern end of the city. The area is covered by dense forest, it is also possible to watch the whole city of Addis.
Thouugh, the new features in the city are numerous, these are among the new features Addis has got in the last three years. This is just to tip on what to expect when coming to Addis for the summit. It is New Year, a new era for Africa, as Africans are committed to endorsing African cause…and Addis is waiting for you, to welcome you to your second home!

አፍሪካዊያን ለኢትዮጵያ ያላቸውን ክብር ያሳዩበት ጉባኤ…



/በሚራክል እውነቱ/

ዛሬ አድገዋል እያልን የምንጠራቸው ሀገራት እዚህ ለመድረሳቸው ዋና ተዋናዮች ዜጎቻቸው ናቸው፡፡ ሀገር እንድትለማም ሆነ እንድትቆረቁዝ የዜጎች እጅ መኖሩ አይቀሬ እውነታ ነው፡፡በጨለማ ውስጥ ከሚታየው ብርሃን ጋር ለመድረስ ህልም ያላቸው ዜጎች ሌት ተቀን ተፍጨርጭረው ድካማቸውን ከቁብ ሳይቆጥሩ በመስራታቸው ከራሳቸው አልፈው ለሀገር ባለውለታ መሆን ችለዋል፡፡

ኢትዮጵያ አነሰም በዛ አሁን ለደረሰችበት ደረጃ መድረስ የዜጎች አሻራ ስለመኖሩ አያጠራጥርም፡፡ምንም እንኳ እንደ አቦሸማኔ መምዘግዘግ ሲገባን ከውስጥም ከውጪም በየጊዜው በሚፈጠሩ ምክንያቶች የተነሳ ፍጥነታችን ቀንሶ በምንፈልገው ልክ ህዝብ የሚሻውን ከፍ ያለ ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት ባይቻልም፡፡

እንደ ሰለጠኑት ሀገራት ከተራራው ጫፍ ላይ ለመድረስ ዛሬን ሰዓት ሳንቆጥር ድካማችንን ሳናስተዋል፣ልዩነቶቻችን ለአገር ልማት እንቅፋት ሳይሆኑን ፣ካለፈው ታሪካችን ተምረን ለትውልድ የምናወርሰው ስራ ሰርተንና ለዚሁ የሚሆን መሰረት ማስቀመጥ ይኖርብናል፡፡ለዚህ የሚያስፈልገው ደግሞ የሌሎች ይሁንታ ሳይሆን የእያንዳንዳችን ተነሳሽነት በመሆኑ እንቅፋት የሚሆን አንዳች ነገር አይኖርም፡፡

ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር የተፈጠረው ለውጥ በርካታ ዜጎችን ያስደሰተ እንደነበር መስካሪ አያሻም፤ምንም እንኳ በምንፈልገው ፍጥነት ልክ እንዳንጓዝ ከጎታች አስተሳሰቦችና ድርጊቶች በተጨማሪ አሸባሪው የህወኃት ቡድን የለየለት የአገር ክህደት ተግባር ሌላኛው ውስጣዊ ፈተና ቢሆንም፡፡

የልማት ስራዎቻችን ረስተን ሁሌም ስለ ጦርነት ማውራት ለባሰ ድህነት ያጋልጣል እንጂ አንድ እርምጃ ወደፊት ሊያራምደን አይችልም፡፡ይህን እውነት በአግባቡ መረዳት ይገባል፡፡ለዚህ ደግሞ ራስን በሚገባ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ልማት እንጂ ጦርነት ለአገርም ሆነ ለህዝብ የሚያመጣው አንዳች ውጤት አይኖርም፡፡

ሉዓላዊነትና የአገር ዕድገት ተነጣጥለው ሊታዩ የሚችሉበት ዕድል አለ ተብሎ አይታሰብም፤ምክንያቱም ከድህነት የማንወጣ ከሆነ ሉዓላዊነታችንን የሚዳፈሩ ጠላቶች ይበዛሉ፤ለዚህ ደግሞ በትናንቱ ታሪክ ሳንቆዝም ነገን አስበን መስራት አለብን፡፡

ስለዚህ ሁላችንም ሀገራችን የምንወድና ከድህነት አዘቅት ወጠን በልማት ጎዳና ላይ መራመድ ከፈለግን ከጦርነት አዙሪት መውጣትና ከመንግስታችን ጎን ተሰልፈን በየተሰማራንበት የስራ መስክ ሀላፊነታችንን በየኔነት መንፈስ ልንወጣና የድርሻችንን ልናበረክት ይገባል ባይ ነኝ፡፡

ኢትዮጵያዊነት ከፍ ያለ ስነ ልቦና ነው፤ለሀገር ውለታ ራሳቸውን መስዋዕት ያደረጉ አባቶች ደምና አጥንት ውጤት ነው፤ኢትዮጵያዊነት ከራስ አልፎ ስለሌሎች ማሰብ ነው፤ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም ቅድሚያ መስጠት ነው፡፡ኢትዮጵያዊነት ሰብዓዊነት፣ትሁትነት፣ቻይነትና አክባሪነት ነው፡፡ኢትዮጵያዊነት መግባቢያ ቋንቋንችን ነው፡፡

ከመጋረጃው ጀርባ የሚታዩ አያሌ የብልጽግና ትሩፋቶች አሉ፤ እርግጥ ነው ይህን ወጋገን በቀላሉ መመልከት ላይቻል ይችላል፡፡ ብዙ መልፋት፣ብዙ መጣር፣ብዙ መስራት እንዲሁም እጃችን እስኪሻክር ድረስ ሌት ተቀን መታተር ከቻልን ፣ከየኔነት ይልቅ የእኛነትን ማስቀደም ስንጀምር፣ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን አድርገን በጋራ ለጋራ ልማት መነሳት ስንችል በርግጥም የምንፈልገውን የብልጽግና ወጋገን ያለከልካይ መመልከት እንችላለን፡፡

በየትኛውም ዓለም በለውጥ ጊዜ ችግሮች መፈጠራቸው አንዱ የለውጡ አካል ወይም ባህሪ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡እናት በእርግዝና ወቅት ያንን ፋታ የማይሰጥ ምጥ ችላ ልጅ እንምትወልደው ሁሉ ሀገራችን ላይ የሚገጥሙን ተግዳሮቶች ሁሉ በድል ማሸነፋችን አይቀሬ ነውና ትንሽ መታገስ ጥሩ ነው፡፡

እኛ ኢትዮጵያዊያን በህብረ ብሔራዊነት የተጋመድን ህዝቦች ነን፡ህብረ ብሔራዊነታችን ኩራታችን፣ አንድታችንና ጥንካሬያችን ከሆነ ይህንኑ መልካም ዕድልና አጋጣሚ ለአገራዊ ልማትና ብልጽግና በማዋል ነገ ሉዓላዊነቷ የማይደፈርና የምትከበር አገር እንድትኖረን ዛሬን መስራት ይኖርብናል፡፡ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ወይንም የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ ስለሆነች ብቻ ከድህነት ልናወጣት አንችልም ፡፡

ይልቁንም ከድህነት ጠኔ ወጥተን አንገታችንን በኩራት ቀና አድርገን ለመኖር ከፈለግን ብሎም ሀገራችንን ከልብ የምንወዳት ከሆነ ከልባችን ሌት ተቀን ሰርተን ገፅታዋን ልንቀይርላት ይገባል ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የእያንዳንዳችን አሻራ ያረፈባት የአንድነታችን ውጤት መሆን ይኖርባታልና ፡፡

ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውኗል።

ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውኗል።
20/05/2014ዓ.ም
ኮልፌ ወረዳ 6 ብልጽግና ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን


የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የ6 ወር የፓርቲ እና የመንግስት ስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ነው።በክፍለ ከተማው አጠቃላይ የተሰሩ የፓርቲ እና የመንግስት ስራዎች ከእቅድ አንጻር አፈጻጸማቸው ተቀምጧል።

ለአገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል ማነቆ የሆኑ ጉዳዮች ውስብስብ በመሆናቸው በተለመደው መንገድ ሳይሆን በእዉቀትና በመረጃ ላይ የተመሰረተ መልኩ ሊፈታ እንደሚገባም ተመላክቷል።

በአጠቃላይ በ6 ወሩ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የቀረበው ሪፖርት ያመለክታል።
ከተቀመጠው እቅድ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም ያመጡ ተቋማት ተመስግነዋል። በአንጻሩ ዝቅተኛ አፈጻጸም የነበራቸው በቀሪ ጊዜ የሚያካክስ ስራ መስራት እንደሚገባ ተመላክቷል።

Design a site like this with WordPress.com
Get started