“በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ፣ ከሬሚታንስና ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ተገኝቷል” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ

በ2014 በጀት ዓመት ከአገልግሎት እና ሸቀጥ የወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) እንዲሁም ከሬሚታንስና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ መገኘቱን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ፡፡

 ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው ዓመት የአገልግሎትና የሸቀጦች ኤክስፖርት ከ10 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ተገኝቷል። ይህ የወጪ ንግድ ገቢ ሬሚታንስንና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ሲጨምር ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር ገደማ የሚጠጋ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውጪ ንግዱ ዘርፍ የተገኘው ውጤት እምርታ የታየበት መሆኑን ጠቁመው፤ እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሆነን የመጣ ውጤት በመሆኑ ሁላችንም በተገኘው ውጤት ልንኮራ ይገባል ብለዋል።

በማክሮ ኢኮኖሚ የዕድገት አመላካቾች ከግሽበት በስተቀር በሁሉም ዘርፍ የተገኘው እምርታ በእጅጉ ይበል የሚያስብልና የሚያኩራራ እንዲሁም ይበልጥ እንድንተጋ የሚያነሳሳ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፤ ሆኖም ኢትዮጵያ ያላት የኤክስፖርት እምቅ አቅም አኳያ ከተገኘው በብዙ እጥፍ መሥራትና ማሳደግ የሚቻል መሆኑን ጠቁመዋል።

የወጪ ንግድን(ኤክስፖርትን) ሳያሳድጉ ሀገርን ማሳደግ እንደሚከብድ ጠቁመው፤ ምንም እንኳን የማክሮ ኢኮኖሚ የዕድገት አመላካቾች በርካታ ቢሆኑም የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴው በኤክስፖርት ምን አመጣሁ ብሎ በዋናነት የሚገመግመው የወጪ ንግድ ለሌሎች ሴክተሮች ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ ነው ብለዋል።

መንገድ፣ ግብርና እና የመሳሰሉት ዘርፎች የሚደገፉትና የሚነቃቁት ሥራቸውን ከውነው ዕድገት የሚያመጡት በውጪ ንግድ በሚገኘው ገቢ መደገፍ ሲቻል እንደሆነም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል አረንጓዴ አሻራ ላይ ትምህርት ሰጪ እና ሕዝቡን የሚያስመሰግን ሥራ መሠራቱን እንዲሁም የቱሪዝም ሀብቶች ላይ ተመሳሳይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በአራት ዓመታት ውስጥ 25 ቢሊዮን ችግኝ መትከል መቻሏን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለጠጥ አድርጎ ከታቀደ በአራት ዓመት ውስጥ ኢትዮጵያ ምን ማድረግ እንደምትችል ያስገነዘበ ትምህርት መቀሰሙን ጠቁመዋል።

እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ገለፃ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳካው የአረጓዴ አሻራ(ግሪን ሌጋሲ) ውጤት በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ሕዝቡ ለተከታታይ ዓመታት ምንም ክፍያ ሳያገኝ የሠራው ሥራ አስደማሚ ነው። ወደ ብልጽግና የሄዱ ሀገራት በሙሉ ታሪካቸው ሲታይ ስሙ ግሪን ሌጋሲ አይባል እንጂ የብልፅናቸው ጅማሬ ከችግኝ ተከላ የሚጀምር ነው።

በብልጽግና ጅማሯችን አሁን የምንከተለው አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ ላለው ትውልድ ላይገባው እንደሚችል ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ ከዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ብልጽግና ሲረጋገጥ ትውልድ ማየት የሚፈልገው አንዱ ነገር አረንጓዴ ሥፍራዎችን ነው። ይህ ደግሞ ሊሳካ የሚችለው ዛሬ ችግኞችን ስንተክል ነው ብለዋል።

በአረንጓዴ አሻራ ተግባራዊ በማድረግ (በግሪን ሌጋሲ) የታየው ውጤት የሚያበረታታ እና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑንም ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብም በግሪን ሌጋሲ ላይ በሠራው ሥራ ሊመሰገንና ሊደነቅ የሚገባው መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከቱሪዝም ዘርፉ አንፃርም ብዙ ሥራዎች እንደሚጠበቁ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፤ በዘርፉ እንደ ኢትዮጵያ ሊሸጥ የሚችል መልክዓ ምድርና ታሪክ ያለው ሀገር ባይኖርም የአገልግሎት ኢንዱስትሪውን ማዘመን ስላልቻልን እየተጠቀምንበት አይደለም ብለዋል።

በቱሪዝም ዘርፍ ያሉትን መስህቦች በመጠቀም በዘርፉ ከፍተኛ እምርታ ሊመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል። ለአብነት ኢትዮጵያ አንድ ተራራ ለአንድ ሪዞርት ፖሊሲን ብትከተል በበርካታ አካባቢ ያሉ መልክዓ ምድሮቿን በመጠቀም ሀገሪቱን የቱሪስት መስህብ ማድረግ እንደሚቻል አመልክተዋል።

ውብሸት ሰንደቁ

አዲስ ዘመን ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም

ችግሮቻችንን ከስር ከስር እየነቀልን #ኢትዮጵያን በማጽናት ላይ እንረባረብ!


************
አገራችን ኢትዮጵያ በታሪክ መዝገብ ውስጥ በደማቅ ቀለም ተጽፋ የምትገኝ፤ ከአለም ስልጣኔ በፊት የስልጣኔ ባለቤት የነበረች የመቻቻል እና የብዝሃነት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ናት ሲባልም እንደው በቃል ብቻ ለማለት ሳይሆን በተጨባጭ ታላቅነቷን የሚመሰክሩ በርካታ መገለጫዎች ስላሏት ጭምር ነው።

ኢትዮጵያን በማንም ሃይል ፍላጎትም ሆነ ንግግር ዝቅ ማድረግ እንዳይቻል አድርገው ከፍ ያደረጓት አባቶቻችንን ስብዕና ተላብሰን እና አገር ከፍ ስትል ከፍ የሚለው የዜጎቿ ክብር መሆኑን በመገንዘብ ሁሌም ቢሆን እንደታሪካችን ንግግራችንም ተግባራችንም ኢትዮጵያን የሚመጥን ሊሆን ይገባል፡፡

ኢትዮጵያን ለማሻገር በሚደረገው የትግል ምዕራፍ የሚገጥሙ ችግሮች ሁሉ በጽናታችን ልክ የምንሻገራቸው እንጂ ወደፊት ከመገስገስ የሚያቆሙን ሊሆኑ አይገባም፡፡ የትናንት ታሪካችን የሚያስተምረን ይሄንኑ ነውና፡፡ በመሆኑም ዛሬም፣ ነገም፣ ወደፊትም በጽናት በመቆም ትኩረታችን ችግሮቻችንን ከስር ከስር እየነቀሉ ኢትዮጵያን ማጽናት ላይ ሊሆን ይገባል፡፡

የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሚቻለውም ችግር የማይበግረውና በአገራዊ ጥቅሙ የማይደራደር ጽኑ ትውልድ በመገንባት ብቻ ነው፡፡

ለብልጽግና የሚሆን ዘር ከመዝራት አልፈን ፍሬ ያፈራ ዛፍም መፍጠር ችለናል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ

ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ ለማዳከም በርካታ ማዕቀቦች ተጥለዋል፤ከአጎዋ ገበያ እንድትወጣ ተደርጓል፡፡ የዓለም ባንክና ሌሎች አበዳሪ አገራት ኢትዮጵያ ብድር እንዳታገኝ ብዙ ጥረቶች አድርገዋል፡፡

ልማታችንን ሊያፋጥኑ የሚችሉ ድጋፎች በአብዛኛው እንዲቆሙ ተደርገዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህና መሰል ፈተናዎች ኢትዮጵያን ወደኋላ ከመመለስ ይልቅ ብርታት ሆነው እነሆ ባለፉት አራት የለውጥ ዓመታት በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችለናል፡፡

ለብልጽግና የሚሆን ዘር ከመዝራት አልፈን ፍሬ ያፈራ ዛፍም መፍጠር ችለናል። በነዚህ ችግሮች ውስጥ አልፈን ስኬት ካመጣንባቸው ስራዎቻችንም ውስጥ የግብርና ዘርፉ ተጠቃሽ ነው፡፡

በዚህ መሰረት ግብርናን ለማዘመን በተሰራው ስራ ከሚታረሰው መሬት ውስጥ 28 ከመቶ በትራክተር ማረስ ተችሏል፤ 45 ከመቶ በኩታ ገጠም ማረስ ተችሏል፡፡

የበጋ ስንዴ ላይ የተሰራው ስራም ለወዳጅ ሃሴት ሲሆን የጠላቶቻችንን አንገት የሚያስደፋ ነው፡፡ ለዘመናት ስንዴ ስትለምን ለኖረች አገር ስለስንዴ ኤክስፖርት ማውራት በራሱ ትልቁ የድል ብስራት ነው፡፡

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ

እያለሙ የሚለሙበት ትውልድ ተሻጋሪ አገልግሎት

ዜማ ያሬድ

አንድ ሰው ከውልደቱ እስከ እድገቱ ባለው ጊዜ የራሱ፣ የቤተሰቡ፣ የአካባቢው፣ ብሎም በትምህርት ቤት ህይወቱና በቅርበት የሚመለከተው ባህሪ ውህድ ውጤት ነው፡፡ ከዚህ አኳያ አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ከቤተሰቡ ከወረሰው ባህሪ ብቻ ሳይሆን በዙሪያው የሚያድግበት አከባቢም ተጽዕኖ ያሳድርበታል፡፡ የሰው ልጅ በአካል፣ በስነምግባርና በእውቀት መልማት የሚችለው ከልጅነት ጀምሮ በሚያልፋቸው መንገዶች መሆኑ የሚያጠያይቅ ጉዳይ አይሆንም፡፡ ሰውን መርዳትና ለሰው መኖርም አብሮ ከሚወለድ ሰውኛ ባህሪ ባሻገር ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከሚከተሉት እምነትና ከሚያራምዱት የህይወት ፍልስፍና የሚቀዳና የሚለመድ መልካም ምግባር ነው፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም ከራስ ውስን ሃብት ቆርሶ ለሌላ የሚሰጥ ጊዜ፣ ጉልበትና እውቀት በመሆኑ በዚህ መልካም ምግባር ውስጥ ለመሳተፍ የበጎ ፈቃደኛው ማንነትና እምነት ወሳኝ ነው፡፡

በአገራችን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፅንሰ ሃሳብና ጠቀሜታን በክረምት በሚደረግ መርሃ ግብር ብቻ ተወስኖ የቆየ ቢሆንም አሁን አሁን በወጣቱ ዘንድ በተለይ ባህል ወደመሆን እየተሸጋገረ መጥቷል፡፡ በአገራችን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያለበት ሁኔታ በተለያየ ፈርጁ የሚጠቀስ ነው፡፡ በግልና በቡድን ሆነው አልያም የበጎ አድራጎት ተቋማት ጋር በመሆን በተለይ የሰው ድጋፍ የሚፈልጉና አቅመ ደካማ የሆኑ ሰዎችን በሆስፒታሎች የሚገኙ ህሙማን የሚንከባከቡ በጎ ፈቃደኞች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ጎዳና የወደቁ ወገኖቻችን የሚያነሱ፤ የተራዙትን የሚያለብሱ፣ የተራቡትን የሚያበሉ በርካታ ወጣቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡

በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከክረምት መርሃ ግብር ወጥቶ ሰፋ ባለ ሁኔታ አመቱን ሙሉ በመተግበር ለአገር ገፅታና ለህብረሰተባዊ ለውጥ በዘላቂነት መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በአገራችን የበጎፈቃድ አገልግሎት እንደዜግነት ግዴታ ተወስዶ ሁሉም እንዲሳተፍ የሚያበረታታ አሰራር ቢፈጠር የተሻለ ለውጥ ማምጣት ይቻላል የሚል እምነት አለኝ፡፡

ወጣቶቹ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መሰማራታቸው የሚኖረውን ህብረተሰባዊ ፋይዳ በሚገባ በማስረዳትና በማደራጀት የአገር አቅም እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቃል፡፡ አገራችን የበርካታ ወጣቶች አገር ሆና ሳለ ወጣቶችን በአግባቡ መጠቀም አለመቻል ትልቅ አገራዊ አቅምን እንደማባከን መሆኑን በመረዳት ለነገ ሳይባል በስር ነቀል የአስተሳሰብ ለውጥ በመታገዝ ወደ ተሻለ ሁኔታ መሻገር መቻል አለበት፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድ ወቅት የለብ ለብ ስራ ብቻ ሳይሆን መሆን ያለበት ዓመቱን ሙሉ ወጣቱ እያሰበበት የሚቆይና የዜግነት ግዴታውና ማህበራዊ ሀላፊነቱ አድርጎ የሚወስደው መሆን አለበት፡፡ ከክረምት ጊዜው ባለፈ በዓመቱ ያለውን የእረፍት ጊዜ ማህበረሰቡን ማገልገል ላይ ሊያውለው ይገባል፡፡ ይህ ጉዳይ አገራዊ በሆነ እቅድና መነቃቃት መመራት ጭምር ይገባዋል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አገር መገንባት ላይ ሊያተኩር ይገባል፡፡ ስለ ኢትዮጵያዊ አንድነትና ወንድማማችነት ማስተማር፣ ኢትዮጵያዊነትን መገንባት ላይ ያተኮሩ ህብረተሰባዊ ማነቃቃቶች ላይ በመስራት ለአገር ግንባታ የሚጠቅም መሰረት መጣል ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የበጎ ፈቃደኝነት ስራ ትልቅ መድረክ ነዉ፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከችግኝ ተከላ እና ከክረምት ትምህርት ማስተማር መሻገር መቻል አለበት፡፡ ወጣቱን ስለአንድነት ማስተማር አለበት፡፡ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲታሰብ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም ወደ ሰው አዕምሮ ግንባታ ጭምር መምጣት አለበት፡፡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሰፋ ብሎ መታሰብ አለበት፡፡

የበጎ ፍቃድ አገልግሎትን ለብልጽግና ጉዞ መሳካትና ለህብረተሰባዊ ለውጥ ወሳኝ በመሆኑ ለዛ መጠቀም ይገባል፡፡

መንግስት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን የሚያበረታቱ አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር አሰራሮችን በመዘርጋትና የበጎ ፈቃደኞችን በማበረታታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ፋይዳ በማብራራት ለህበረተሰባዊ ለውጥ ለመጠቀም መትጋት ይገባዋል፡፡ አገራችን እንደሌላ አገራት ዜጎች በበጎ ፈቃድ አገልገሎት መስክ የሚሰማሩ ወጣቶችን በማስፋትና ከአገር አቀፍ ወደ አህጉር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳደግ ሌሎች አገሮችን ጭምር ሄዶ ማገልገል የሚችል ሰብዓዊነትን የተላበሰና የፓን አፍሪካኒዝም ጽንሰ ሀሳብን የሚያቀነቅን ዜጋ እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል፡፡

የግልና የመንግስት ተቋማት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ተሰማርተው ህብረተሰባቸውን ሲያገለግሉ ለነበሩ ወጣቶች በስራ ገበታም ሆነ ተያያዥ ጉዳዮች ቅድሚያ በመስጠትና ከሁሉ በላይ ተግባራቸዉን በማበረታታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እያለሙ የሚለሙበት ዋጋ ያለው የህይወት ዘመን ሰናይ መስክ መሆኑን በተጨባጭ መደገፍ ይገባል፡፡

እያለሙ የሚለሙበት ትውልድ ተሻጋሪ አገልግሎት

ዜማ ያሬድ

አንድ ሰው ከውልደቱ እስከ እድገቱ ባለው ጊዜ የራሱ፣ የቤተሰቡ፣ የአካባቢው፣ ብሎም በትምህርት ቤት ህይወቱና በቅርበት የሚመለከተው ባህሪ ውህድ ውጤት ነው፡፡ ከዚህ አኳያ አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ከቤተሰቡ ከወረሰው ባህሪ ብቻ ሳይሆን በዙሪያው የሚያድግበት አከባቢም ተጽዕኖ ያሳድርበታል፡፡ የሰው ልጅ በአካል፣ በስነምግባርና በእውቀት መልማት የሚችለው ከልጅነት ጀምሮ በሚያልፋቸው መንገዶች መሆኑ የሚያጠያይቅ ጉዳይ አይሆንም፡፡ ሰውን መርዳትና ለሰው መኖርም አብሮ ከሚወለድ ሰውኛ ባህሪ ባሻገር ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከሚከተሉት እምነትና ከሚያራምዱት የህይወት ፍልስፍና የሚቀዳና የሚለመድ መልካም ምግባር ነው፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም ከራስ ውስን ሃብት ቆርሶ ለሌላ የሚሰጥ ጊዜ፣ ጉልበትና እውቀት በመሆኑ በዚህ መልካም ምግባር ውስጥ ለመሳተፍ የበጎ ፈቃደኛው ማንነትና እምነት ወሳኝ ነው፡፡

በአገራችን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፅንሰ ሃሳብና ጠቀሜታን በክረምት በሚደረግ መርሃ ግብር ብቻ ተወስኖ የቆየ ቢሆንም አሁን አሁን በወጣቱ ዘንድ በተለይ ባህል ወደመሆን እየተሸጋገረ መጥቷል፡፡ በአገራችን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያለበት ሁኔታ በተለያየ ፈርጁ የሚጠቀስ ነው፡፡ በግልና በቡድን ሆነው አልያም የበጎ አድራጎት ተቋማት ጋር በመሆን በተለይ የሰው ድጋፍ የሚፈልጉና አቅመ ደካማ የሆኑ ሰዎችን በሆስፒታሎች የሚገኙ ህሙማን የሚንከባከቡ በጎ ፈቃደኞች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ጎዳና የወደቁ ወገኖቻችን የሚያነሱ፤ የተራዙትን የሚያለብሱ፣ የተራቡትን የሚያበሉ በርካታ ወጣቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡

በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከክረምት መርሃ ግብር ወጥቶ ሰፋ ባለ ሁኔታ አመቱን ሙሉ በመተግበር ለአገር ገፅታና ለህብረሰተባዊ ለውጥ በዘላቂነት መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በአገራችን የበጎፈቃድ አገልግሎት እንደዜግነት ግዴታ ተወስዶ ሁሉም እንዲሳተፍ የሚያበረታታ አሰራር ቢፈጠር የተሻለ ለውጥ ማምጣት ይቻላል የሚል እምነት አለኝ፡፡

ወጣቶቹ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መሰማራታቸው የሚኖረውን ህብረተሰባዊ ፋይዳ በሚገባ በማስረዳትና በማደራጀት የአገር አቅም እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቃል፡፡ አገራችን የበርካታ ወጣቶች አገር ሆና ሳለ ወጣቶችን በአግባቡ መጠቀም አለመቻል ትልቅ አገራዊ አቅምን እንደማባከን መሆኑን በመረዳት ለነገ ሳይባል በስር ነቀል የአስተሳሰብ ለውጥ በመታገዝ ወደ ተሻለ ሁኔታ መሻገር መቻል አለበት፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የአንድ ወቅት የለብ ለብ ስራ ብቻ ሳይሆን መሆን ያለበት ዓመቱን ሙሉ ወጣቱ እያሰበበት የሚቆይና የዜግነት ግዴታውና ማህበራዊ ሀላፊነቱ አድርጎ የሚወስደው መሆን አለበት፡፡ ከክረምት ጊዜው ባለፈ በዓመቱ ያለውን የእረፍት ጊዜ ማህበረሰቡን ማገልገል ላይ ሊያውለው ይገባል፡፡ ይህ ጉዳይ አገራዊ በሆነ እቅድና መነቃቃት መመራት ጭምር ይገባዋል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አገር መገንባት ላይ ሊያተኩር ይገባል፡፡ ስለ ኢትዮጵያዊ አንድነትና ወንድማማችነት ማስተማር፣ ኢትዮጵያዊነትን መገንባት ላይ ያተኮሩ ህብረተሰባዊ ማነቃቃቶች ላይ በመስራት ለአገር ግንባታ የሚጠቅም መሰረት መጣል ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የበጎ ፈቃደኝነት ስራ ትልቅ መድረክ ነዉ፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከችግኝ ተከላ እና ከክረምት ትምህርት ማስተማር መሻገር መቻል አለበት፡፡ ወጣቱን ስለአንድነት ማስተማር አለበት፡፡ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲታሰብ ችግኝ መትከል ብቻ አይደለም ወደ ሰው አዕምሮ ግንባታ ጭምር መምጣት አለበት፡፡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሰፋ ብሎ መታሰብ አለበት፡፡

የበጎ ፍቃድ አገልግሎትን ለብልጽግና ጉዞ መሳካትና ለህብረተሰባዊ ለውጥ ወሳኝ በመሆኑ ለዛ መጠቀም ይገባል፡፡

መንግስት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን የሚያበረታቱ አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር አሰራሮችን በመዘርጋትና የበጎ ፈቃደኞችን በማበረታታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ፋይዳ በማብራራት ለህበረተሰባዊ ለውጥ ለመጠቀም መትጋት ይገባዋል፡፡ አገራችን እንደሌላ አገራት ዜጎች በበጎ ፈቃድ አገልገሎት መስክ የሚሰማሩ ወጣቶችን በማስፋትና ከአገር አቀፍ ወደ አህጉር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳደግ ሌሎች አገሮችን ጭምር ሄዶ ማገልገል የሚችል ሰብዓዊነትን የተላበሰና የፓን አፍሪካኒዝም ጽንሰ ሀሳብን የሚያቀነቅን ዜጋ እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል፡፡

የግልና የመንግስት ተቋማት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ተሰማርተው ህብረተሰባቸውን ሲያገለግሉ ለነበሩ ወጣቶች በስራ ገበታም ሆነ ተያያዥ ጉዳዮች ቅድሚያ በመስጠትና ከሁሉ በላይ ተግባራቸዉን በማበረታታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እያለሙ የሚለሙበት ዋጋ ያለው የህይወት ዘመን ሰናይ መስክ መሆኑን በተጨባጭ መደገፍ ይገባል፡፡

ብልጽግና እንደተባለው ለሁሉም በሁሉም ከሁሉም የሆነ ፓርቲ ነው፡፡

ብልጽግና እንደተባለው ለሁሉም በሁሉም ከሁሉም የሆነ ፓርቲ ነው፡፡ብልጽግናን ኢትዮጵያ ውስጥ ማረጋገጥ ከፈለግን ፣ኢትዮጵያን በልዕልና ማማ ላይ ማቆም ከፈለግን፣ኦሮሞው፣አማራው፣ትግሬው፣ ሲዳማው፣ ሱማሌው፣ አፋሩም፣ ወላይታው፣ ስልጤም፣ ጉራጌም፣ ጉሙዙ ሌሎች ህዝቦችም በእኩልነት ለሁለንተናዊ ልማት ስንሳተፍና መጠቀም ስንችል ብቻ ነው፡፡

መላው የብልጽግና ቤተሰቦች ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና መውጣት የምትችለው ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በእኩልነት፣በፍቅር፣በወንድማማችነት ተከባብረው፣ተፈቃቅደው ተዋደው መትጋት ሲችሉ ብቻ በመሆኑ መረዳት እና በአንድ ልብና መንፈስ ተሳስረን ሁሉንም የምንጠቅም፣ሁሉንም የምናገለግል፣ሁሉን የምንወድና ለሁሉም የምንቆም መሆናችንን በተግባር ማሳዬት ይኖርብናል፡፡

በብልጽግና እሳቤ በግልጽ የተቀመጠ ቢሆንም ዋናው ፍላጎታችን ግን ኢትዮጵያን በከፍታ ማማ ላይ ነግሳ ማዬት ነው፡፡የምናስበው ቦታ ለመድረስ ደግሞ እልህ አስጨራሽ ፈተና፣ወገብ የሚያጎብጥ የሌት ተቀን ስራ፣እሾህ አሜካላውን ማለፍ ይጠበቅብናል፡፡ዛሬ በሰራነው መልካም ስራ ለመጪው ትውልድ ያደገችና የበለፀገች ሀገር ማውረስ ያስችለናል፡፡

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት

https://facebook.com/kolfeworedasix.prosperityparty1

ብልጽግና የኢትዮጵያዊነት ባህሪን የያዘ ህዝባዊ ፓርቲ


/በሚራክል እውነቱ/


ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ በልጆቿ ብርታት አጠናክራ ቀጥላለች፡፡ ማንም የራሱን የፖለቲካ አጀንዳ ከአገርም ሆነ ከሕዝብ ሊያስበልጥ አይችልም፡፡ የትኛውም ሃይል ከኢትዮጵያዊነት ከፍታ ሊያወርደን አይደለም ትልቁን የኢትዮጵያዊነት ምሥል እንዲያደበዝዝ አንፈቅድለትም፡፡
ምክንያቱም ሃገር ከምንም ትልቃለች፡፡ በሃገራዊ አንድነት ጥላ ስር ተሰብስበን ለሃገራዊ ለውጥ የምንተጋበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ይህንን ቃል በመፈጸም በህዝብ ዘንድ የተጣለበትን እምነትና አደራ ይወጣል፡፡
ዓለም ወደ አንድ መንደር እየተሰበሰበች ባለችበት በዚህ ዘመን ከወንድማማችነት ይልቅ ልዩነትን የሚያቀነቅኑ ሃይሎች በብልጽግና ዘመን ቦታ የላቸውም፡፡ ብልጽግና ሕብረ-ብሔራዊ ሆና በተገነባች ኢትዮጵያ ላይ አንዱን ከፍ ሌላውን ዝቅ የሚያደርግ አካሄድ መቼም አይከተልም፡፡ ይህን ለማድረግ ፍላጎት ያላቸው ሀይሎች ካሉም በጽናት ይታገላል፡፡ የፓርቲው ፕሮግራምና ህገ ደንብ በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውል ተገቢውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ለተግባራዊነቱ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳያል፡፡
ብልጽግና የኢትዮጵያዊነት ባህሪን የያዘ ህዝባዊ ፓርቲ ነው፡፡ ይህ ማለት እርስ በእርስ መተሳሰብን፣ መተጋገዝን፣ አንድነትንና ወንድማማችነትን የመሰሉ የቆዩ ኢትዮጵያዊ እሴቶቻችንን ለማስቀጠል የሚሰራ ወቅቱን የዋጀ ፓርቲ ነው፡፡ አመራሩም ሆነ አባሉ እነዚህን ኢትዮጵያዊ እሴቶች ጠብቆ ለትውልድ የማስተላለፍ አደራ ተጥሎበታል፡፡ ከእዚህ አኳያ አመራሩም ሆነ አባሉ በፓርቲው ፕሮግራምና ህገ ደንብን ተከትሎ የሚመራ ይሆናል፡፡
ለዘመናት በተካሄደ ትግል በልጆቿ በተገነባች ኢትዮጵያ ውስጥ በዴሞክራሲና በነፃነት እየኖሩ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እገዛ ከማድረግ እና የብልጽግና ጉዟችንን ከማፋጠን ይልቅ ከውስጥም ከውጭም በባዕዳን ነዋይ ተደልለው በገዛ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ላይ የጸረ-አንድነት መፈክር በማሰማት ህዝብ የሚፈልገውን አገራዊ ዕድገት ለማስተጓጎል ጥረቶችን አድርገዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን በማጎልበት ለእንደዚህ አይነቱ ተራ የእልቂት ነጋሪት ምላሽ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ጥላቻን በጥላቻ ሳይሆን ማሸነፍ የሚቻለው ጥላቻን በፍቅር እንደሆነ ብልጽግና ፓርቲ ያምናል፡፡ ይህ ደግሞ ፓርቲው በህዝብ ዘንድ የገባውን ቃል ለመወጣት ያግዘዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት ያዳበረውን ፍቅር፣ መከባበርና መደጋገፍ እንደገና ወደነበረበት በማስቀጠል አንዱ ጎታች ሌላው ተጎታች ሳይሆን ወይም አንዱ የበላይ ሌላው የበታች ሳይሆን ሁሉም እኩል ለሀገሩ ብልፅግና አሻራውን የሚያሳርፍበት ወቅት እንዲሆን ፓርቲው ፕሮግራሞቹንና ህገ ደንቦቹን ተከትሎ እየሰራ ይገኛል፡፡
ብልፅግና ፓርቲ ከሰራቸው ስራዎችና ካመጣቸው ለውጦች ይልቅ ገና ወገብ የሚያጎብጡ ዘመን ተሻጋሪ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ውጤት ለማምጣት ርብርብ እያደረገ የሚገኝ ፓርቲ ነው፡፡ ምክንያቱም ብልፅግና በዕውቀትና በዕውነት ላይ የቆመ ፓርቲ ነውና፡፡ ብልጽግና ህልሙ ትልቅና ሰፊ እንጂ በትንንሽ ነገሮች ረክቶ የሚቀመጥ ፓርቲ እንዳልሆነ ካስቀመጣቸው ፕሮግራሞችና ህገ ደንቦች መረዳት ይቻላል፡፡
አገራዊ አጀንዳን በአግባቡ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ብልጽግና ፓርቲ ከማንም የተደበቀ አጀንዳ የለውም፡፡ አጀንዳው ልማት ነው፡፡ ብልጽግና ነው፡፡ ትንንሽ ልዩነቶቻችንን በማቻቻል፣ ከጎጠኝነትና ከቡድንተኝነት አስተሳሰብና ድርጊት በመውጣት እና ለሃገርና ለሃገራዊ አንድነት ቅድሚያ መስጠት ከቻልን በእርግጥም የበለጸገች ኢትዮጵያን በጋራ ድካማችን መገንባት እንችላለን፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ለአሁኑ ትውልድ ብቻ ሳይሆን ነገን ተሻግሮ ለመጪው ትውልድ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ዛሬን እየሰራ ያለ ፓርቲ ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ፓርቲው ለአገርና ለህዝብ የማይከፍለው መስዋዕትነት የለም፡፡ ምክንያቱም ሀገር ከሁሉም ትልቃለችና፡፡

Prosperity

“ጥላቻን በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር ልናሸንፈው ይገባል…”


በሚራክል እውነቱ
::::::::::::::።።።።።።።።።።:::::::::::::
የኢትዮጵያ ሰላም፣ፍቅርና አንድነት በልጆቿ መዳፍ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ይህ ከሆነ ታዲያ ምን ያህሎቻችን በሰከነ አዕምሯችን ተረድተነው ይሆን? እስኪ ወደ ራሳችን ተመልሰን ከልብ እናጢነው፡፡

እርግጠኛ መሆን ባይቻልም ብዙዎቻችን ግን ከተራ ትርጉም በዘለለ ሀያልነታቸውን አስበነው አናውቅም፡፡የዚህ ትርጉም  በጥልቀት መረዳት የሚችሉት እንደነ ሶሪያ፣ሊቢያ፣የመንና በቅርቡ ሰላሟ እንደራቃት እንደ ጎረቤታችን ሱዳን የመሳሰሉት ሀገራት ናቸው፡፡

ሀገር በእልህ ሳይሆን በጥበብ፣በንግግር ሳይሆን በተግባር፣በዘልማድ ሳይሆን በዕውቀት፣በጥድፊያ ሳይሆን በእርጋታ ነው ልትመራ የምትችለው፡፡ነገር ግን ምርጫችን ከዚህ በተቃራኒው በመሆኑ ምክንያት ሀገሪቱ አይታው በማታውቀው ሁኔታ ብሔርንና ማንነትን መሰረት በማድረግ አንዱ አካባቢ በሌላው አካባቢ በሚኖሩ ሰዎች ላይ ክብራቸውንና ማንነታቸውን በሚያጎድፍ መልኩ ዘለፋ፣ ፉከራና አጉል ጀብደኝነት በቃላትና በምስል አስደግፈው በዘመን አመጣሹ ፌስ ቡክ፣ቲዊተርና በሌሎችም የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት ሲለጥፉት የሚስተዋለው፡፡

ታዋቂው የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በአንድ ወቅት እንዲህ ሲል መናገሩ ይታወቃል፤ “Darkness cannot drive out darkness; only light can do that. Hate cannot drive out hate; only love can do that”. ጨለማን በጨለማ ሳይሆን በብርሀን፤ ጥላቻንም በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር ልንቀይረው እንደሚገባን ያሳየናል፡፡

ታዲያ እውነታው ይህ ከሆነ እኛ እየሆን ያለነው የትኛውን ነው? ጥላቻን በጥላቻ ወይስ ጥላቻን በፍቅር? ማንም ሊረዳው የሚገባው እውነታ ግን ጥላቻ የበለጠ ሰውን ከሰው እያራራቀ ወዳልተፈለገ መንገድ ይመራል እንጂ ሰላምና አንድነትን ከቶውንም ቢሆን አምጥቶ አያውቅም፡፡

ስለዚህ በሰዎች ዘንድ የቱንም ያህል ክብራችንን የሚነካ ማንነታችንን የሚያጠለሽ ነገር እንኳ ቢፈጠር ክፉን በክፉ መመለስ ሳይሆን መጥፎውን በደግነት ቀይረን እኛነታችንን የበለጠ በመልካምነት ልናሳይ ይገባናል፡፡

ኢትዮጵያዊነት በጊዜያዊ ተግዳሮቶች ተሸንፎ ከውድድር ውጭ መሆን ሳይሆን ያጋጠሙትን እክሎች ወደ  መልካም አጋጣሚዎች  በመቀየር ድል ማድረግ ሲቻል ነው።ከዚህ ውጭ ትርጉም ሊኖረውም አይችልም፡፡

የአብሮነትና የዘመናዊነት ተምሳሌት ኢትዮጵያ፤ ዘመናትን በስልጣኔ ማማ የነገሰች ኢትዮጵያ ፣የህዝባችን የከፍታና ኩራት መሰላል፤ እጅግ ውብ ባህል እና  የዘመን አይሽሬ እሴቶቻችን ባለቤት፤ኢትዮጵያችን የታሪክ አውድማ እና የኩሩ ህዝብ ምድር መሆኗን አለም ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ሀቅ ነው፡፡

ለዚህም ነው ጥላቻና ዘረኝነትን ጉድጓድ ቀብረን በሰዎች መካከል መተሳሰብ፣ፍቅር፣አንድነትና የአብሮነት ስሜት እንዲፈጠር በማድረግ የምንሳሳላትና ከማንም በላይ ቅድሚያ ለምንሰጣት ሀገራችን ያለንን ክብርና ፍቅር በተግባር ልናሳያት ይገባል የሚባለው፡፡  Prosperity Party – ብልፅግና

የማኅበራዊ ፕሮግራም — #ጤናመከላከልን መሠረት ያደረገ የጤና ሥርዓት መዘርጋት

#Ethiopia

  1. ፓርቲያችን በዋናነት በሽታን በመከላከል ላይ የተመሠረተ የጤና ጥበቃ ሥርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል። በተጨማሪም አክሞ የማዳን ዐቅምን በዘላቂነት ለማሳደግ የሰው ኃይል፣ ሥርዓትና ቴክኖሎጂ ዐቅም ግንባታ ላይ ፓርቲያችን ቅድሚያ ይሰጣል።
  2. ፓርቲያችን ለእናቶችና ሕጻናት ጤና ክብካቤ ልዩ ትኩረት በመስጠት ይሠራል የሴቶች ጤና የሥነ ተዋልዶ ጤና ችግር ለመቅረፍ፣ ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶች እንዲወገዱ እና አጠቃላይ የሴቶችን ጤና ለመጠበቅ ከቅድመ ወሊድ እስከ ድኅረ ወሊድ ድረስ በአቅራቢያቸው በጤና ተቋማት አገልግሎት እንዲያገኙ ፓርቲያችን ይታገላል። ሀገራችን በጤና ዘርፍ ወደ ኋላ የቀረችባቸዉን ዘርፎች አንዱ የሆነው የጨቅላ ሕፃናት ጤና እንክብካቤ ትኩረት እንዲሰጠው ይሠራል።
  3. በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ያሉ ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ የነጻ ሕክምና አገልግሎት የሚሰጥበት አሠራር እንዲዘረጋ ያደረጋል። ከዚህም በተጨማሪ የጤና መድኅን ሽፋን በመላ ሀገራችን እንዲዳረስ አሠራርን በማዘመን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ደረጃውን የጠበቀ የጤና መድኅን ሽፋን ተጠቃሚ እንዲሆን ያደረጋል።
  4. ፓርቲያችን ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና የሥነ ሕዝብ ፓሊሲ መሠረት ነው ብሎ ያምናል። ፓርቲያችን የሕዝብ ቁጥሩ ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገታችን ጋር ተመጣጥኖ እንዲሄድ እንዲሁም ጤናማ የሆነ ኅብረተሰብ ለመፍጠር የሚያስችል በፍላጎት ላይ የተመሠረተ የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራሞች እንዲዘረጉ ያደርጋል።
  5. የሕክምና ባለሞያዎች ፍልሰትን በተለይም ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ የባለሞያዎችን ፍልሰት ለመቀነስ በገጠር የሚሠሩ ባለሞያዎችን ልዩ ጥቅምን ይሰጣል።
  6. የሕክምና ቁሳቁስ እጥረትን ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል። የሕክምና ቁሳቁሶች በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ የሚደረግበት ዐቅም እንዲፈጠር ፓርቲያችን ይሠራል።
  7. የባህል ሕክምና እንዲዘምን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከዘመናዊ ሕክምና ጋር እንዲደጋገፍና በጥናትና ምርምር እንዲልቅ ያደረጋል።
    Addis Ababa Prosperity Party – ብልፅግና Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ Ministry of Health,Ethiopia Mayor Office of Addis Ababa

የብልጽግና ፓርቲ ማህበራዊ ፕሮግራሞችየማኅበራዊ ፕሮግራም ግቦች — #ትምህርትሀ. ፍትሐዊነት፣ ጥራት፣ አካታችነት እና አግባብነት ያለው የትምህርት ሥርዓት ማረጋገጥ

  1. በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የትምህርት ተደራሽነትና ፍትሐዊነት ለማረጋገጥ ፓርቲያችን ይታገላል። በዚህም መሠረት የቅደመ መደበኛ ትምህርት በሀገራችን ሙሉ ለሙሉ እንዲዳረስ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሠራ ይደረጋል፡፡
  2. ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተደራሽና ፍትሐዊ በማድረግ በኩል የአንደኛ ደረጃና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት /ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል/ ሁሉም ዜጐች ትምህርት እንዲያገኙ ፓርቲያችን ይታገላል፡፡ ለዚህም ሀገራዊ ስታንደርዳቸውን የጠበቁና በቴክኖሎጂ የተደገፉ ትምህርት ቤቶች ሕዝቡን በማሳተፍ እንዲሠሩ ይደረጋል፡፡ በሌላ በኩል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ኢኮኖሚው በሚፈልገው መልኩ በሦስት ዘርፎች ማለትም የአጠቃላይ ትምህርት፣ መሠረታዊ የቴክኒክና ሞያ እንዲሁም በልዩ ተሰጥዖ ትምህርት ተደራጅቶ እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡
  3. አሁን ያለውን የሀገራችን ዕድገት በጐልማሳው ትከሻ ላይ የወደቀ በመሆኑ የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጐልማሶች ትምህርት ጐልማሳው የራሱን ሕይወት እንዲቀይር ብሎም በሀገሪቱ ዕድገት ላይ ትርጉም ያለው አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ለማድረግ ኘሮግራሙ ተቃኝቶ ተግባራዊ እንዲሆን ፓርቲያችን ይታገላል፡፡
  4. ፓርቲያችን በዋናነት የትምህርት ተደራሽነትን አረጋግጦ በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች የትምህርት ጥራትን ማሳደግ የትምህርት ፕሮግራሙ ዋነኛ ዓላማ አደርጎ ይታገላል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ክሂሎትን መሠረት ያደረገ፣ የሀገር በቀል ዕውቀት ያካተት፣ ዜጐች ችግር ፈቺና ተመራማሪ ሆነው እንዲገነቡና ለሀገራቸው ብልጽግና የሚተጉ እንዲሆኑ፤ መምህራን በተሻለ ችሎታና ሥነ ምግባር የታነፁ ሆነው ትውልድን በዕውቀት፣ በክሂሎት እና በመልካም ሥነ ምግባር የሚቀርፁ፣ እንዲሁም የሚገባቸውን ሞያዊ ክብርና ጥቅም እንዲያገኙ ሀገራዊ የመምህራን ልማት ኘሮግራም በማሻሻል ፓርቲያችን ይሠራል።
  5. የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ሥልጠና የውጤት ተኮር ሥርዓት መሠረት በማድረግ እስካሁን በሀገራችን እየተተገበረ ያለ ቢሆንም በተለያዩ ያተገባበር ችግሮች ምክንያት የተፈለገውን ውጤት አላመጣም፡፡ በአተገባበር የታዩ ችግሮችንና ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የኢንዱስትሪውን የሠለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ለመሙላት በሚያስችል መልኩ እንዲደራጅ ያደርጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት፣ ዐቅማቸው እንዲጎለብት ተደርጎ ለኢንዱስትሪው የጀርባ አጥንት የሆነ ብቃት ያለው የሰው ኃይል እንዲያመርቱ ከማድረግ ባሻገር ለቴክኖሎጂ ሽግግር ከፍተኛ ሚና እንዲጫወቱ ያደርጋል።
  6. የሀገራችን ከፍተኛ ትምህርት ከኢንዱስትሪው የሰው ኃይልና የምርምር ፍላጎት ጋር ትሥሥርና አግባብነት ያለው እንዲሆን ፓርቲያችን ይሠራል። የከፍተኛ ትምህርት ቅበላ ሥርዓቱ የተማሪዎችን ፍላጎትና ዝግጁነት ግምት ውስጥ በማስገባት የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎትና ዐቅምን ባገናዘበ መልኩ እንዲቀረፅ ያደርጋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተለየ ተልዕኮ ላይ አተኩረው፤ ከማስተማር ሥራ ባሻገር ጥናትና ምርምር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ላይ በማተኮር ለኅብረተሰቡ ችግር መፍትሔ የሚሰጡ ሆነው ተልዕኳቸውን እንዲወጡ ይደረጋል፡፡ በተጨማሪም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የዕውቀትና የጥበብ መናኸሪያዎች፣ ብዝኃነትን የሚያጎለብቱና እርስ በእርስ መቀራረብን የሚፈጥሩ የዓለም አቀፋዊ ዕሴቶችና አስተሳሰቦች ማዕከላት እንዲሆኑ ፓርቲያችን አበክሮ ይሠራል።
  7. ፓርቲያችን ሁሉም የትምህርት ተቋማት የአካዳሚ ነጻነትን ከሚያቀጭጩ ፖለቲካዊም ሆነ ከአስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነቶች ነጻ እንዲሆኑ በማድረግ፣ በዕለት ተዕለት የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የኅብረተሰብ አገልግሎት ሥራ ሁሉም ዕይታዎች በእኩል መድረክ አግኝተው በነጻነት የሚንሸራሸሩባቸው እንዲሆኑ ይሠራል።
  8. የሥነ ምግባርና ሥነ ዜጋ ትምህርት አብሮነትን በማሳደግና ግብረ ገባዊ ዕሴቶችን በማስፋትና በማስረፅ በመልካም ሥነ ምግባር የታነፀ ሀገር ወዳድ ትውልድ በማፍራት ረገድ የሚጫወተው ሚና እጅግ የላቀ እንደሆነ ፓርቲያችን ይረዳል። ስለዚህ የተማሪዎችን ባህሪያት መልካም ለማድረግ የግብረ ገብ ትምህርት እስከ 6ኛ ክፍል ራሱን ችሎ እንዲሁም ከ7ኛ ክፍል በኋላ በሥነ ምግባርና ሥነ ዜጋ ትምህርት ተካቶ ሀገራዊ አብሮነትን እና ኅብረ ሀገራዊነትን የሚያጠናክር፣ የሀገር ፍቅርን የሚያፀና እና ግብረ ገብነትን የተላበሰ ትውልድ መፍጠሪያ ተደርጎ እንዲቀረፅ ያደርጋል።
  9. ፓርቲያችን በአንደኛ ደረጃና በመካከለኛ ደረጃ የትምህርት ቋንቋ ብዝኃ ልሳን እንዲሆን የሚያደርግ ሲሆን ብዝኃ ልሳንነቱ የምንገነባውን ኅብረ ሀገራዊ አንድነትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ከክልሎች ነባራዊ ሁኔታ ጋር በሚጣጣም መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል።

#ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች መቻቻል የሰፈነባት አብነታዊ አገር ነች።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ይህንን አንድነት ለመሸርሸርና በሃይማኖት ሽፋን የአገሪቱን ልማት ለማደናቀፍና የህዝቧን አንድነት ለመበተን የነበራትን የሠላም እሴት ለመናድ ያልተቆጠበ ጥረት ሲደረግ ይታያል፡፡

በሀገራችን የሃይማኖት ተከታዮች በሠላም አብሮ የመኖር መልካም እሴት ባለቤት መሆናቸውን በመግለፅ ከአባቶቻችን የወረስነው ይህን ትልቅ ሃብት ጠብቀን ለሚቀጥለው ትውልድ የማስተላለፍ ሃላፊነትና አደራን መወጣት ከሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል የሚጠበቅ ጉዳይ ነው።

በሠላም አብሮ የመኖር እሴቶቻችንን የሚሸረሽሩ የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ዝንባሌዎች እየተስተዋሉ ነው፤ አክራሪነትና ጽንፈኝነት በምንም መልኩ ሃይማኖታዊ መሠረት የለውም።

ከፀረ ዴሞክራሲያዊ አመለካከትና ተግባር የሚመነጨው አክራሪነትና ጽንፈኝነት መነሻም ሆነ መድረሻው ኪራይ ሰብሳቢነትና በአቋራጭ የፖለቲካ ስልጣን በመያዝ መንግስታዊ ሃይማኖት ወይም ሃይማኖታዊ መንግስት ለመመስረት እንደሆነ አያጠያይቅም።

የሃይማኖት የጋራ እሴቶች አለማክበር ወይም አለመጠበቅ የሃይማኖት ባለቤት ሆኖ ከሃይማኖተኝነት ውጪ መሆን ወይም ሃይማኖት አለኝ እያሉ በሃይማኖት ስም ከሃይማኖተኝነት ውጪ የሆኑ ድርጊቶችን መፈፀም ማለት ነው። ሰላማዊ አለመሆን፣ ርህራሔ ማጣት፣ ራስህንና ማህበረሰቡን ለብጥብጥና ለሁከት መዳረግ፣ በራስ እምነት ውስጥ ያሉ አማኞችን አንዱን አጥባቂ ፣ አንዱን ፅንፈኛ፣ ሌላውን ገድየለሽና ግብዝ እያደረጉ በመቁጠር የራስን ጥቅምና ፍላጎት ለመፈፀም መጣር ማለት ነው።

ሃይማኖታዊ የጋራ እሴቶች ካልተከበሩ በአማኞችና በህብረተሰቡ ዘንድ መንፈሳዊና ማህበራዊ፣ ሃይማኖታዊና ዓላማዊ ችግሮችን በማስፋት ልዩነቶችን፣ ጥላቻን፣ ብጥብጥን፣ ሁከትን ለመጠፋፋት የሚያደርስ ግጭትን ያስከትላልና ቆም ብለን የቆምንበትን ስፍራ መመርመር ይገባል።

Prosperity

Design a site like this with WordPress.com
Get started